በተደጋጋሚ የሚጠየቁ ጥያቄዎች

  • 01የኢትዮጵያ ነጋዴዎች የምክክር መድረክ አላማው ምንድን ነው?

    የዚህ መድረክ ዋነኛ አላማ በሃገራችን ያሉ የቤተሰብ ቢዝነሶችን ዘመን ተሻጋሪ ፣ ጠንካራና ተፎካካሪ እንዲሆኑ የሚያስችልና ፤ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አውድ ላይ የተመሰረተ የአመራርና አስተዳደር እውቀቶችንና ልምዶችን የሚካፈሉበት መድረክ መሆን ነው።

  • * የሀገራችንን የቤተሰብ ቢዝነሶች በተመለከተ ቋሚ ምርምሮችን ማካሄድ ፣ የምርምሮቹን ውጤት መሰረት በማድረግ ለተለያዩ የቤተሰብ ቢዝነስ ተግዳሮቶች እንደ ተሰማሩበት ኢንዱስትሪ ሀገራዊ መፍትሄዎች የሚዳሰሱበት አመታዊ ፎረም ማዘጋጀት ፤

    * አለምአቀፍ ተሞክሮዎች ላይ የተመረኮዙ ፣ በተለያዩ የቤተሰብ ቢዝነስ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑና ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚሰጡ ስልጠናዎችንና ወርክሾፖችን በተለያዩ ጊዜያት ማዘጋጀትና

    * እንደ አስፈላጊነቱ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ የቤተሰብ ቢዝነሶች የሚገናኙበት ፣ የሚወያዩበትና የሚመክሩበት መድረኮችን ማዘጋጀት ናቸው።

  • * መሰረታቸው ቤተሰብ የሆነ እና በንግዱ ስራ ለረዥም ጊዜ ቆይተው ስለ ንግዳቸው የወደፊት ዕጣ ፈንታ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እያሰቡ ያሉ ተቋማትና

    * ንግዱን ከመሰረቱት ባለቤቶች ተረክበው የንግዱን ስራ በማስቀጠል እየሰሩ ያሉ ተረካቢ ትውልዶች ናቸው።

  • የቤተሰብ ንግድ ባለቤቶች ፣ የንግድ ስራ ትምህርት ቤቶች ፣ በቤተሰብ የንግድ ስራ ምርምር ላይ የሚሰሩ ተቋማት ፣ ከንግዱ ስራ ጋር ግንኙነት ያላቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና የፋይንስ ተቋማት ናቸው።

  • ኤች ኤስ ቲ ኮንሰልቲንግ ፒ ኤል ሲ የፎረሙ አዘጋጅ ሲሆን ዋነኛ የፎረሙ ተዋናዮች ግን የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት የቤተሰብ ቢዝነሶች ናቸው።